በአገር አቀፍ ደረጃ አዲስ የኮቪድ-19 ማዕበል መከሰቱን የኢትዮጵያ ህብረተሰብ ጤና ኢንስቲቲዩት አስታወቀ
በአገር አቀፍ ደረጃ አዲስ የኮቪድ-19 ማዕበል መከሰቱን የኢትዮጵያ ህብረተሰብ ጤና ኢንስቲቲዩት አስታውቋል፡፡
ኢንስቲቲዩቱ ሰሞኑን በተከሰተው ጉንፋን መሰል ወረርሽኝ ዙሪያ ማብራሪያ ሰጥቷል፡፡
በማብራሪያውም ሰሞኑን የተከሰተውን ጉንፋን መሰል ወረርሽኝን ተከትሎ በአንዳንድ ተቋማት በተወሰደ የናሙና ምርመራ ከ59 እስከ 86 በመቶ የሚሆኑት የኮሮና ቫይረስ እንደተገኘባቸው ጠቁሟል፡፡
ኢንስቲቲዩቱ ባለፉት 15 ቀናትም በተለይ በአዲስ አበባ የኮቪድ-19 ስርጭት በስፋት መስተዋሉን ነው የገለጸው፡፡
ወደጤና ተቋማት ሄደው ከተመረመሩት ከ55 ሺህ በላይ ሰዎች ከ25 ሺህ በላይ የሚሆኑት ኮቪድ-19 እንደተገኘባቸው ተመላክቷል፡፡
እንደ አገር ከሁለት ሳምንት በፊት 5 በመቶ የነበረው በኮቪድ19 የመያዝ ምጣኔ አሁን ላይ ወደ 36 በመቶ ከፍ ማለቱም በማብራሪያው ተጠቁሟል፡፡
ዜጎች "የጉንፋን ወረረሽኝ" ከሚለው መዘናጋት