በጋና የቁንጅና ውድድር ኢትዮጵያን በመወከልና በማስተዋወቅ የተሳተፈችው ጋናዊት አዲስ አበባ ገባች
በጋና የኢትዮጵያን ታሪክ፣ ባህል በመወከልና በማስተዋወቅ የተሳተፈችው ዶክተር ሴቶር ኖርግቤ አዲስ አበባ ገባች።
ጋናዊቷ የሜዲካል የአዕምሮ ህክምና ባለሙያና ደራሲ ዶክተር ሴቶር ኖርግቤ የኢትዮጵያን ታሪክ ፤ስልጣኔ፤ባህላዊ አልባሳት በጋና የቁንጅና መድረክ ላይ በማስተዋወቅ የሀገሯን የቁንጅና ውድድር የመጀመሪያ ዙር ማሸነፏ ይታወቃል።
በጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ ጥሪ መሰረት በርካታ ዳያስፖራዎች ወደ ሀገር ቤት እየገቡ ይገኛሉ በዚህ ጥሪ የኢትዮጵያ ወዳጆችና አፍሪካውያን ጭምር እየተሳተፉ ወደ ኢትዮጵያ እየገቡ ይገኛል።
በሀገሯ ጋና የቁንጅና ውድድር ላይ ኢትዮጵያን በማስተዋወቅ ለኢትዮጵያ ያላትን ልዩ ፍቅር የገለጸቸው ጋናዊቷ የሜዲካል የአዕምሮ ህክምና ባለሙያና ደራሲ ዶክተር ሴቶር ኖርግቤ ዛሬ ምሽት አዲስ አበባ ገብታለች።
የኢትዮጵያ ወዳጇ ዶክተር ሴቶር በቦሌ አለም አቀፍ አየር ማረፊያ ስትደርስም በታዋቂ ሰዎ