በጋና የቁንጅና ውድድር ኢትዮጵያን በመወከልና በማስተዋወቅ የተሳተፈችው ጋናዊት አዲስ አበባ ገባች

በጋና የኢትዮጵያን ታሪክ፣ ባህል በመወከልና በማስተዋወቅ የተሳተፈችው ዶክተር ሴቶር ኖርግቤ አዲስ አበባ ገባች።

ጋናዊቷ የሜዲካል የአዕምሮ ህክምና ባለሙያና ደራሲ ዶክተር ሴቶር ኖርግቤ የኢትዮጵያን ታሪክ ፤ስልጣኔ፤ባህላዊ አልባሳት በጋና የቁንጅና መድረክ ላይ በማስተዋወቅ የሀገሯን የቁንጅና ውድድር የመጀመሪያ ዙር ማሸነፏ ይታወቃል።

በጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ ጥሪ መሰረት በርካታ ዳያስፖራዎች ወደ ሀገር ቤት እየገቡ ይገኛሉ በዚህ ጥሪ የኢትዮጵያ ወዳጆችና አፍሪካውያን ጭምር እየተሳተፉ ወደ ኢትዮጵያ እየገቡ ይገኛል።

በሀገሯ ጋና የቁንጅና ውድድር ላይ ኢትዮጵያን በማስተዋወቅ ለኢትዮጵያ ያላትን ልዩ ፍቅር የገለጸቸው ጋናዊቷ የሜዲካል የአዕምሮ ህክምና ባለሙያና ደራሲ ዶክተር ሴቶር ኖርግቤ ዛሬ ምሽት አዲስ አበባ ገብታለች።

የኢትዮጵያ ወዳጇ ዶክተር ሴቶር በቦሌ አለም አቀፍ አየር ማረፊያ ስትደርስም በታዋቂ ሰዎ

Only people mentioned by Ferew in this post can reply

No replys yet!

It seems that this publication does not yet have any comments. In order to respond to this publication from Ferew Abebe, click on at the bottom under it