ኢትዮጵያዊው ዳኛ ባምላክ ተሰማ ለአፍሪካ ዋንጫ ለማለፍ የሚደረገውን ወሳኝ ጨዋታ በዋና ዳኝነት ይመራል

ኢትዮጵያዊው ዳኛ ባምላክ ተሰማ ለአፍሪካ ዋንጫ ለማለፍ የሚደረገውን ወሳኝ የግማሽ ፍጻሜ ጨዋታ በዋና ዳኝነት እንደሚመራ የአፍሪካ እግር ኳስ ኮንፌዴሬሽን (ካፍ) አስታወቀ።

33ኛው የአፍሪካ ዋንጫ ለግማሽ ፍጻሜ ያለፉ አራት አገራት ነገ እና ከነገ በስቲያ ጨዋታቸውን የሚያደርጉ ሲሆን፤ በነገው እለት ምሽት አራት ሰዓት ቡርኪናፋሶ ከሴኔጋል ጨዋታቸውን ያደርጋሉ፡፡

ካፍ እንዳስታወቀው፤ ለፍጻሜ ለማለፍ የሚደረገውን ይህን ጨዋታ ኢትዮጵያዊው ዳኛ ባምላክ ተሰማ በዋና ዳኝነት ይመራዋል፡፡

በተጨማሪ ሱዳናዊው ሙሀመድ አብዱላሂና ኬኒያዊው ጊልበርት ችሮይት ደግሞ በረዳትነት ዳኝነት ጨዋታውን የሚመሩት ይሆናል፡፡

ከነገ በስቲያ ምሽት አራት ሰዓት ደግሞ የውድድሩ አስተናጋጅ ካሜሩን እና ግብጽ ጨዋታቸውን እንደሚያደርጉ ይታወቃል፡፡(ENA)

Only people mentioned by Ferew in this post can reply

No replys yet!

It seems that this publication does not yet have any comments. In order to respond to this publication from Ferew Abebe, click on at the bottom under it