ኮሚሽነር ለሊሴ ነሜ “ለዓመቱ ምርጥ የአፍሪካ ወጣት” ሽልማት በእጩነት ቀረቡ

የኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ኮሚሽን ኮሚሽነር ለሊሴ ነሜ “በፊውቸር አፍሪካ የዓመቱ ምርጥ ወጣት” ሽልማት ውስጥ በእጩነት ቀረቡ።

አፍሪካውያን ወጣቶችን በማስተሳሰር የአህጉሪቷን ችግሮች ለመቅረፍ የሚንቀሳቀሰው “ዘ ፊውቸር አፍሪካ” ፕሮጀክት የ16ተኛውን ዘ ፊውቸር ሽልማት እጩዎችን ይፋ አድርጓል።

ታዋቂው የእግር ኳስ ተጫዋች ሞሐመድ ሳላህን ጨምሮ አምስት አፍሪካውያን በተካተቱበት የእጩዎች ዝርዝር ውስጥ የኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ኮሚሽነር ለሊሴ ነሜም ተካተዋል።

ለሽልማቱ በእጩነት መመረጣቸውን ተከትሎ ኮሚሽነሯ ባስተላለፉት መልዕክት “በሽልማቱ እጩ ዝርዝር ውስጥ በመካተቴ ከፍተኛ ደስታ ይሰማኛል፣ ለፕሮጀክቱም ምስጋናዬን አቀርባለሁ” ብለዋል።

በእጩነት ከቀረቡት ውስጥ የዚምቧቡዌና የናይጄሪያ ስራ ፈጣሪዎችና ተጽዕኖ የሚያሳድሩ ወጣቶች ይገኙበታል።

መቀመጫውን በሌጎስ ናይጄሪያ አድርጎ የሚንቀሳቀሰው “ዘ ፊውቸር አፍሪካ” አፍሪካውያን ወጣቶችን በማስተሳሰር በአፍሪካ አንገብጋቢ የሆኑትን የመልካም አስተዳደርና የስራ አጥነት ችግርን ለመፍታት እንደሚንቀሳቀስ መረጃዎች ያሳያሉ።

(ኢዜአ)

Only people mentioned by go_61f3d7b43b65c in this post can reply

No replys yet!

It seems that this publication does not yet have any comments. In order to respond to this publication from dibora tadesse, click on at the bottom under it