የአርቲስት ኒና ግርማ ማጀቴ የሙዚቃ አልበም ነገ ይለቀቃል

"ማጀቴ" የተሰኘው አዲስ የሙዚቃ አልበም በመጪው ሐሙስ ለአድማጭ ይደርሳል።

በሻኩራ ሪከርድስ የተዘጋጀው "ማጀቴ" የተሰኘው  አልበም   ሀሙስ የካቲት 10 ቀን 2014 ዓ.ም ለአድማጭ እንደሚደርስ አዘጋጆቹ ትላንት በቀነኒሳ ሆቴል  በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ ይፋ አድርገዋል።

ይህ አልበም የራፕ ዘፈኖችን በማቀንቀን  የምትታወቀው ኒና ግርማ የመጀመሪያ አልበም ሲሆን፥ በማኅበራዊ ጉዳዮች ላይ ያተኮሩ ስራዎችንም አካቷል።

በካሙዙ ካሳ የተቀናበረው  የማጀቴ አልበም የግጥም እና ዜማ ድርሰት በኒና ግርማ የተሰራ እንደሆነና በሻኩራ ሪከርድስ አማካይነት ፕሮዲዩስ እንደተደረገም ተገልጿል።

Only people mentioned by Ferew in this post can reply

No replys yet!

It seems that this publication does not yet have any comments. In order to respond to this publication from Ferew Abebe, click on at the bottom under it