የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባላት ለጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ ምስጋና አቀረቡ
የኢፌዲሪ የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ በህልውና ዘመቻው ወቅት በግንባር ዘምተው ላበረከቱት አስተዋጾ ምስጋና አቅርበዋል።
ለጠቅላይ ሚኒስትሩ ጥያቄዎችን እያቀረቡ ያሉት የምክር ቤቱ አባላት ጥያቄያቸው ከማቅረባቸው አስቀድመው ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ በህልውና ዘመቻው ወቅት ግንባር ዘምተው የአገር አንድነትን ለማስጠበቅ ለከፈሉት ዋጋ ምስጋና አቅርበዋል።
ብዙዎቻችን ኢትዮጵያን እንወዳለን እንላለን እርስዎም ይላሉ እርስዎ ግን በተጨባጭ ግንባር ዘምተው የአገር አንድነትን ያስጠበቁ ስለሆነ ምስጋና ይገባዎታል ሲሉም አባላቱ ለጠቅላይ ሚኒስትሩ ምስጋና አቅርበዋል።
በአሁኑ ወቅት የምክር ቤቱ አባላት ጥያቄያቸውን እያቀረቡ ናቸው።
(ኢ ፕ ድ)