የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባላት ለጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ ምስጋና አቀረቡ

የኢፌዲሪ የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ በህልውና ዘመቻው ወቅት በግንባር ዘምተው ላበረከቱት አስተዋጾ ምስጋና አቅርበዋል።

ለጠቅላይ ሚኒስትሩ ጥያቄዎችን እያቀረቡ ያሉት የምክር ቤቱ አባላት ጥያቄያቸው ከማቅረባቸው አስቀድመው ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ በህልውና ዘመቻው ወቅት ግንባር ዘምተው የአገር አንድነትን ለማስጠበቅ ለከፈሉት ዋጋ ምስጋና አቅርበዋል።

ብዙዎቻችን ኢትዮጵያን እንወዳለን እንላለን እርስዎም ይላሉ እርስዎ ግን በተጨባጭ ግንባር ዘምተው የአገር አንድነትን ያስጠበቁ ስለሆነ ምስጋና ይገባዎታል ሲሉም አባላቱ ለጠቅላይ ሚኒስትሩ ምስጋና አቅርበዋል።
በአሁኑ ወቅት የምክር ቤቱ አባላት ጥያቄያቸውን እያቀረቡ ናቸው።

(ኢ ፕ ድ)

Only people mentioned by go_61f3d7b43b65c in this post can reply

No replys yet!

It seems that this publication does not yet have any comments. In order to respond to this publication from dibora tadesse, click on at the bottom under it