የጤና ሚኒስትሯ ዶክተር ሊያ ታደሰና የዓለም የምግብ ድርጅት የሥራ ሃላፊዎች ቦረና ዞንን እየጎበኙ ነው
የጤና ሚኒስትሯ ዶክተር ሊያ ታደሰና የዓለም የምግብ ድርጅት የሥራ ሃላፊዎች ቦረና ዞንን እየጎበኙ ነው።
ልዑካን ቡድኑ በጉብኝታቸው ድርቁ ያስከተለውን ጉዳት እንደሚመለከቱ ይጠበቃል።
በቦረና ዞን ለተከታታይ ወቅቶች ዝናብ ባለመጣሉ የተከሰተው ድርቅ ቁጥሩ ከፍ ያለ የዞኑ ነዋሪን ለምግብ እህል እጥረት የዳረገ ሲሆን፥ በከብት ሀብት ላይ የከፋ ጉዳት አድርሷል።(ኤፍ ቢ ሲ)