በአፋር የተከፈተው ጥቃት የኢትዮጵያን ገጽታ ለማጠልሸት ያለመ ነው₋ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ
ሰሞኑን በአሸባሪው ህወሃት በአፋር የተከፈተው ጥቃት ዋናኛ አላማ የኢትዮጵያን ገጽታ ለማጠልሸት ያለመ መሆኑን ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ ገለጹ፡፡
ጠቅላይ ሚኒስትሩ ከህዝብ ተወካዮች ለቀረቡ ጥያቄዎች በሰጡት ማብራሪያ አሸባሪው እና ቁማርተኛው ህወሃት የአለም ሀገራት ኢትዮጵያን ለመክሰስ ያስችላል በሚል ጥቃቱን መክፈቱን ገልጸዋል፡፡
በአፋር የተከፈተው ጥቃት የመላው ኢትዮጵያውን ጥቃት በመሆኑ በጋራ እንከላከለዋለንም ብለዋል፡፡
ለትግራይ ህዝብ ምግብ እና መድሃኒት አለመድረሱ ምንም ደንታ ያሌለው ህወሃት ዋነኛ ስሌቱ ያራሱ ጥቅም ብቻ ማስጠበቅ መሆኑን በግልጽ አሳይቷል ብለዋል፡፡
የአፋር እና የአማራ ህዝብ በወንድም ትግራይ ህዝብ ላይ መንገድ ለመዝጋት ቀርቶ የአሸባሪውን ህወሃት ቁስለኞችን በመንከባከብ ሞራል ያለው ህዝብ መሆናቸውን አሳይተዋል ብለዋል፡፡
በዚህ ጦርነት እንደ ትግራይ ክልል የደቀቀ ክልል የለም የሉት ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ የኢትዮጵያ ህዝብ ትግራይን መልሶ የመገንባት ዕዳ አለበት ብለዋል፡፡(EBC)