"የአድዋን ታሪክ በሚገባ በመለየት አሁን ላለንበት ችግር መፍቻ ቁልፍ ማድረግ ይገባል" - ሂሩት ካሳው (ዶክተር)

የአድዋን ታሪክ በሚገባ በመለየት አሁን ላለንበት ችግር መፍቻ ቁልፍ ማድረግ ይገባል ሲሉ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ባህል ኪነጥበባትና ቱሪዝም ቢሮ ሃላፊ ሂሩት ካሳው (ዶክተር) ገለጹ።

የአድዋ ድል በዓል ለ126ኛ ጊዜ “አድዋን ለኢትዮጵያውያን ኅብረት፣ ለአፍሪካ የነፃነት ጮራ” በሚል መሪ ሃሳብ የሚከበረውን በአል አስመልክቶ የውይይት መድረክ እየተካሄደ ነው።

በዚህ መድርክ ላይ የቢሮዉ ሃላፊው እንደገለጹት፣ አድዋ የነጻነት ድል ብቻ ሳይሆን ፍትህ፣ አርነት፣ ሉአላዊነት የተገኘበት ድል ነው። ይህን በተለየ መንገድ ማየት መጠቀም ያስፈልጋል።

እንደ ዶክተር ሂሩት ንግግር፣ አድዋ ኢትዮጵያ ለአለም ፍትህን ያሳየችበትና በአለም እይታ ውስጥ የገባችበት ድል ነው።

ስለዚህ አድዋን በሚገባ በመረዳት አሁን ላለንበት ችግር የመፍቻ ቁልፍ አድርጐ መጠቀም ያስፈልጋል።
በፓናል ውይይቱ ከአድዋ ምን መማር አለብን፣ ከአድዋ በኋላ ኢትዮጵያ ምን አገኘች፣ ምን ሆነች የሚሉ ጉዳዮችን በጥናታዊ ጹሁፍ ቀርበው ውይይት ይደረግባቸዋል ተብሏል።

በውይይቱ አባትና እናት አርበኞች፣ የከፍተኛ የትምህርት ተቋማት ተወካዮችና ሌሎች ጉዳዩ የሚመለከታቸው አካላት ተገኝተዋል።(ኢ.ፕ.ድ)

Only people mentioned by go_61f3d7b43b65c in this post can reply

No replys yet!

It seems that this publication does not yet have any comments. In order to respond to this publication from dibora tadesse, click on at the bottom under it