"የአድዋን ታሪክ በሚገባ በመለየት አሁን ላለንበት ችግር መፍቻ ቁልፍ ማድረግ ይገባል" - ሂሩት ካሳው (ዶክተር)
የአድዋን ታሪክ በሚገባ በመለየት አሁን ላለንበት ችግር መፍቻ ቁልፍ ማድረግ ይገባል ሲሉ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ባህል ኪነጥበባትና ቱሪዝም ቢሮ ሃላፊ ሂሩት ካሳው (ዶክተር) ገለጹ።
የአድዋ ድል በዓል ለ126ኛ ጊዜ “አድዋን ለኢትዮጵያውያን ኅብረት፣ ለአፍሪካ የነፃነት ጮራ” በሚል መሪ ሃሳብ የሚከበረውን በአል አስመልክቶ የውይይት መድረክ እየተካሄደ ነው።
በዚህ መድርክ ላይ የቢሮዉ ሃላፊው እንደገለጹት፣ አድዋ የነጻነት ድል ብቻ ሳይሆን ፍትህ፣ አርነት፣ ሉአላዊነት የተገኘበት ድል ነው። ይህን በተለየ መንገድ ማየት መጠቀም ያስፈልጋል።
እንደ ዶክተር ሂሩት ንግግር፣ አድዋ ኢትዮጵያ ለአለም ፍትህን ያሳየችበትና በአለም እይታ ውስጥ የገባችበት ድል ነው።
ስለዚህ አድዋን በሚገባ በመረዳት አሁን ላለንበት ችግር የመፍቻ ቁልፍ አድርጐ መጠቀም ያስፈልጋል።
በፓናል ውይይቱ ከአድዋ ምን መማር አለብን፣ ከአድዋ በኋላ ኢትዮጵያ ምን አገኘች፣ ምን ሆነች የሚሉ ጉዳዮችን በጥናታዊ ጹሁፍ ቀርበው ውይይት ይደረግባቸዋል ተብሏል።
በውይይቱ አባትና እናት አርበኞች፣ የከፍተኛ የትምህርት ተቋማት ተወካዮችና ሌሎች ጉዳዩ የሚመለከታቸው አካላት ተገኝተዋል።(ኢ.ፕ.ድ)