የሩሲያ እና ዩክሬን የሰላም ድርድር ዛሬ በቤላሩስ ይጀመራል
የሩሲያ እና ዩክሬን የሰላም ድርድር በዛሬው እለት በቤላሩስ እንደሚጀምር ተገልጿል፡፡
በቤላሩስ የሚደረገው የሁለቱ አገራት የሰላም ድርድር በዩክሬን የሩሲያ ወታደራዊ ዘመቻን ለማስቆም ያለመ ስለመሆኑ ተመላክቷል፡፡
ብዙ የሩሲያ ቋንቋ ተናጋሪዎች ያሏቸውን የዶኔትስክ እና የሉጋንስክ ግዛቶችን ከጸረ-ሩሲያውያን ለመጠበቅ በሚል ሞስኮ በዩክሬን ላይ ወታደራዊ ዘመቻ ከጀመረች ዛሬ ስድስተኛ ቀኑን ይዟል፡፡
ከወታደራዊ ዘመቻው ጥቂት ቀናት በኋላ የዩክሬኑ ፕሬዚዳንት ቮሎድሚር ዘለንስኪ÷ አገራቸው ከሩሲያጋር ለመወያየት ዝግጁ መሆኗን ይፋ ማድረጋቸው ይታወሳል፡፡
ይህን ተከትሎም የሚደረገው ድርድር በአገራቱ መካከል የተጀመረውን ጦርነት ማስቆም ያስችላል በሚል በተስፋ ሲጠበቅ ቆይቷል፡፡
እንደ አር ቲ ዘገባ አገራቱ በዛሬው ዕለት የሰላም ድርድሩን የሚጀምሩ ሲሆን÷ ምክክሩም ከዩክሬን ድንበር አቅራቢያ በምትገኘው ቤላሩስ ከሰዓታት በኋላ ይካሄዳል ተብሎ ይጠበቃል፡፡
የቤላሩስ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴርም የአገራቱን የሰላም ድርድር ለማስጀመር አስፈላጊውን ቅድመ ዝግጅት ማድረጓን አስታውቋል::(ኤፍ ቢ ሲ)