የአዲስ አበባ ትራንስፖርት ቢሮ የፌደራል መንጃ ፈቃድ እድሳት አገልግሎት መስጠት ጀመረ
በአዲሱ የተቋማት አደረጃጀት መሰረት ቀደም ሲል በፌደራል ትራንስፖርት ባለስልጣን ሲሰራ የነበረው የፌደራል መንጃ ፈቃድ እድሳት ከጥቅምት 5/2014 ዓ.ም ጀምሮ ለአዲስ አበባ ከተማ የትራንስፖርት ቢሮ በውክልና ከትራንስፖርትና ሎጂስቲክስ ሚኒስቴር መሰጠቱ ይታወሳል፡፡
በዚህም መሰረት ከህዳር 23/2014 ዓ.ም ጀምሮ የፌደራል መንጃ ፈቃድ እድሳት ከዚህ ቀደም አገልግሎቱ ይሰጥበት በነበረበት በቃሊቲ የአሽከርካሪዎች የማሰልጠኛ ማዕከል ውስጥ አገልግሎቱን መስጠት የጀመረ በመሆኑ ተገልጋዮች አገልግሎቱን ማግኘት እንደሚችሉ ቢሮው አሳውቋል፡፡ #Ethiopia #MejaFikad #AddisAbaba